የኮንስታንቲኖቭካ ነጻ መውጣት የዩክሬንን የዶንባስ የመከላከያ መስመር አፍርሷል - ባለሙያ
09:19 05.07.2026 (የተሻሻለ: 09:24 05.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኮንስታንቲኖቭካ ነጻ መውጣት የዩክሬንን የዶንባስ የመከላከያ መስመር አፍርሷል - ባለሙያ
የኮንስታንቲኖቭካ መያዝ ለሩሲያ ከፍተኛ የኦፕሬሽን እና የሥነ-ልቦና ብልጫ ይሰጣል፤ በዶንባስ ያለውን አጠቃላይ የዩክሬን መከላከያ መዋቅር ሊያፈርስ እንደሚችል ቱርካዊቷ የውጭ ፖሊሲ ባለሙያ ቱባ ቼቢ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
ባለሙያዋ የተናገሯቸው ቁልፍ ነጥቦች፦
ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ፦ ኮንስታንቲኖቭካ፤ ስላቭያንስክ፣ ክራማቶርስክ፣ ድሩዝኮቭካ እና ኮንስታንቲኖቭካን ያካተተው የመከላከያ መስመር ደቡባዊ መልህቅ ነበረች።
የሎጂስቲክስ መስተጓጎል፦ ከተማዋን ማጣት የዩክሬን ጦር በዶኔትስክ ግንባር ለጥይትና ትጥቅ አቅርቦት እንዲሁም ለወታደር ሽግሽግ የሚጠቀምበትን ዋና የባቡር እና የየብስ መንገድ ትስስር መስመር ያቋርጣል።
ለድርድር የሚሰጠው ብልጫ፦ ይህ ታላቅ ስኬት ሩሲያ ዶንባስን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ወደምትፈልገው ግብ ይበልጥ ስለሚያቀርባት፣ በወደፊት ድርድሮች ላይ የሞስኮን አቋም ያጠናክራል። በተጨማሪም በምዕራባውያን ጥምረት ውስጥ በዩክሬን ፖሊሲ ላይ ያለውን ልዩነት ሊያሰፋው ይችላል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X