ፑቲን ለትራምፕ እና ለአሜሪካ ህዝብ በሀገሪቱ የነጻነት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
08:30 05.07.2026 (የተሻሻለ: 08:44 05.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፑቲን ለትራምፕ እና ለአሜሪካ ህዝብ በሀገሪቱ የነጻነት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካው አቻቸው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አዲስ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን የክሬምሊን ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ተናግረዋል።
የስልክ ጥሪው በአሜሪካ ወገን የመጣ ሲሆን ለ1 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ዘልቋል።
በውይይቱ ወቅት ፑቲን፤ ለትራምፕ እና ለመላው የአሜሪካ ህዝብ የአሜሪካ ነጻነት 250ኛ ዓመት ለሚዘከርበት የነጻነት ቀንን በማስመልከት እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል።
የሩሲያው ፕሬዝዳንት በተጨማሪም፤ ሩሲያ ለአሜሪካ የሀገርነት ምሥረታ ያደረገችውን አስተዋጽኦ ያስታወሱ ሲሆን፣ ትራምፕ አሜሪካ እያስተናገደች ባለችው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ቀጣይነት ያለው ስኬት እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X