ጋና በጎርፍ ሳቢያ የሟቾች ቁጥር 34 መድረሱን ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ የጽዳት ዘመቻ ጀመረች - የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት

ሰብስክራይብ

ጋና በጎርፍ ሳቢያ የሟቾች ቁጥር 34 መድረሱን ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ የጽዳት ዘመቻ ጀመረች - የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት

በወታደራዊ ኃይል የሚመራ ከጎርፍ አደጋ በኋላ የመልሶ ማቋቋም እና አደጋን የመቀነስ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝና ለዚህም የተዘጉ የፍሳሽ ማስወገጃዎችን፣ ወንዞችን እና የውኃ ማስተላለፊያዎችን ለማጽዳት የሰው ኃይል፣ መሐንዲሶች እና ከባድ ማሽነሪዎች መሰማራታቸውን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

ዋና ዋና ዝርዝሮች፦

የሟቾች ቁጥር ወደ 34 ያደገ ሲሆን፤ 12ቱ በአክራ ከተማ ብቻ የተመዘገቡ ናቸው። ሪፖርቶች ተጣርተው ሲያልቁ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።

ሰባት ክልሎች በአደጋው የተጠቁ ሲሆን፤ 89,736 ሰዎች ደግሞ ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል።

ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ለአስቸኳይ የእርዳታ ማድረሻ የሚሆን 26.49 ሚሊዮን ዶላር ከተጠባባቂ ፈንድ እንዲለቀቅ አድርገዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0