ጋና በጎርፍ ሳቢያ የሟቾች ቁጥር 34 መድረሱን ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ የጽዳት ዘመቻ ጀመረች - የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት
19:45 04.07.2026 (የተሻሻለ: 19:54 04.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ጋና በጎርፍ ሳቢያ የሟቾች ቁጥር 34 መድረሱን ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ የጽዳት ዘመቻ ጀመረች - የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት
በወታደራዊ ኃይል የሚመራ ከጎርፍ አደጋ በኋላ የመልሶ ማቋቋም እና አደጋን የመቀነስ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝና ለዚህም የተዘጉ የፍሳሽ ማስወገጃዎችን፣ ወንዞችን እና የውኃ ማስተላለፊያዎችን ለማጽዳት የሰው ኃይል፣ መሐንዲሶች እና ከባድ ማሽነሪዎች መሰማራታቸውን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
የሟቾች ቁጥር ወደ 34 ያደገ ሲሆን፤ 12ቱ በአክራ ከተማ ብቻ የተመዘገቡ ናቸው። ሪፖርቶች ተጣርተው ሲያልቁ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።
ሰባት ክልሎች በአደጋው የተጠቁ ሲሆን፤ 89,736 ሰዎች ደግሞ ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል።
ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ለአስቸኳይ የእርዳታ ማድረሻ የሚሆን 26.49 ሚሊዮን ዶላር ከተጠባባቂ ፈንድ እንዲለቀቅ አድርገዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia