የማደጋስካር ፕሬዝዳንት ተሽከርካሪ ባልታወቁ ድሮኖች ሲታደን እንደነበር የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ
19:33 04.07.2026 (የተሻሻለ: 19:34 04.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የማደጋስካር ፕሬዝዳንት ተሽከርካሪ ባልታወቁ ድሮኖች ሲታደን እንደነበር የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ
የማደጋስካር ፕሬዝዳንታዊ አስተዳደር እንዳመለከተው፤ አንደኛው ድሮን ሐሙስ ዕለት የተስተዋለ ሲሆን በቀጣዩ ቀን ደግሞ ተጨማሪ ሁለት ድሮኖች ታይተዋል።
ድሮኖቹ እጅግ በጣም ከፍተኛ በረራ ላይ ስለነበሩ መትቶ ለመጣል እንዳልተቻለም ጽሕፈት ቤቱ አክሎ ገልጿል።
ፕሬዝዳንት ሚካኤል ራንድሪያኒሪና በሰላምና በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ መግለጫው አጽንኦት ሰጥቷል።
ተመሳሳይ ክስተት ሲያጋጥም ይህ የመጀመሪያው አይደለም፤ ባለፈው ሚያዝያ ወር አምስት ድሮኖች በፕሬዝዳንቱ መኖሪያ ቤት ላይ ሲያንዣብቡ ተስተውለው ነበር። በተጨማሪም መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ እና በፕሬዝዳንቱ ላይ የግድያ ሙከራ ለመፈጸም አቅደዋል የተባሉ 13 ሰዎች ክስ ተመስርቶባቸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X