የኪዬቭ አገዛዝ በሌሊት በሩሲያ ግዛት ላይ የተቀናጀ ሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት ለመሰንዘር ሞከረ - የመከላከያ ሚኒስቴር
17:04 04.07.2026 (የተሻሻለ: 17:44 04.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኪዬቭ አገዛዝ በሌሊት በሩሲያ ግዛት ላይ የተቀናጀ ሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት ለመሰንዘር ሞከረ - የመከላከያ ሚኒስቴር
ዘለንስኪ የሀገሪቱን ነዋሪዎች እና የውጭ ስፖንሰሮቻቸውን ትኩረት ለማስቀየር የሞከሩበት ይህ ጥቃት መክሸፉን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። ጥረቱ ሩሲያ ሐሙስ ዕለት በኪዬቭ ወታደራዊ ተቋማት ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት መዘዞች እና በኮንስታንቲኖቭካ ከተማ የደረሰውን የዩክሬን መከላከያ አስከፊ ውድቀት ለመሸፈን የተደረገ እንደነበር ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
የሩሲያ የአየር መከላከያ ሥርዓቶች አሥር የ‘ፍላሚንጎ’ ክሩዝ ሚሳኤሎችን ጨምሮ ከ500 በላይ የአየር ላይ ኢላማዎችን መትተው ጥለዋል። ኪየቭ በጥቃቱ የ‘ሃይማርስ’ ባለብዙ ተወንጫፊ ሮኬት ሥርዓቶችንም ተጠቅማለች።
ዘለንስኪ በሩሲያ የሲቪል ተቋማት ላይ ጉዳት ለማድረስ ያደረገው ሙከራ ተመጣጣኝ የአጸፋ እርምጃ ሳይወሰድበት አይቀርም።
በሰኔ ወር ውስጥ ብቻ በሩሲያ ሰማይ ላይ ወደ 13 ሺህ የሚጠጉ ኢላማዎች ተመትተው የወደቁ ሲሆን፤ ለእነዚህ መሣሪያዎች ምርት እና ማስወንጨፊያ የሚሆን ድጋፍ እንግሊዝን ጨምሮ በአብዛኞቹ የአውሮፓ ኅብረት ሀገራት የሚቀርብ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X