የሩሲያ ጦር ኮንስታንቲኖቭካን መቆጣጠሩ ለሌሎች ስልታዊ ከተሞች መያዝ መንገድ ይከፍታል - የወታደራዊ ጉዳዮች ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የሩሲያ ጦር ኮንስታንቲኖቭካን መቆጣጠሩ ለሌሎች ስልታዊ ከተሞች መያዝ መንገድ ይከፍታል - የወታደራዊ ጉዳዮች ባለሙያ

በዶንባስ ቁልፍ የኢንዱስትሪ እና የትራንስፖርት ማዕከል የሆነችውን ኮንስታንቲኖቭካን ነፃ ማውጣት መቻሉ፤ የሩሲያ ኃይሎች ወደ ምዕራብ አቅጣጫ በመግፋት ወደ ስላቭያንስክ እና ክራማቶርስክ ከተሞች እንዲገሰግሱ በር የሚከፍት መሆኑን በወታደራዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ጥናት ያደረጉት አንጋፋው ሩሲያዊ ምሁር አንድሬ ኮሽኪን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ከባለሙያው ማብራሪያ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

ስልታዊ ጠቀሜታ፦ ኮንስታንቲኖቭካን መቆጣጠር የሩሲያ ኃይሎችን ወደ ዶኔትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ቁልፍ ድንበሮች የሚያስጠጋቸው ሲሆን፤ የውጊያ ግቦችን ለማሳካትም ትልቅ ምዕራፍ ነው።

ለዘለንስኪ የደረሰ የፖለቲካ ምት፦ ከተማዋን ማጣታቸው የአውሮፓ መሪዎችን ዩክሬን በጦር ሜዳ ስኬት እያገኘች መሆኑን ለማሳመን ለሚሞክረው የኪዬቭ አገዛዝ ከባድ የፖለቲካ ውድቀት ነው።

የሰው ኃይል እጥረት፦ ዩክሬን በግምት የ100 ሺህ ወታደሮች ከፍተኛ የሰው ኃይል እጥረት የገጠማት ሲሆን፤ የመከላከያ መስመሯን ለማቆየት ስትል ከሌሎች የጦር ግንባሮች ኃይሏን ለማዛወር መገደዷን ኮሽኪን ጠቁመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0