የምዕራብ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ‘የአፍሪካ ዓይን’ የተሰኘውን የአቡጃ ዋና መሥሪያ ቤቱን ይፋ አደረገ

ሰብስክራይብ

የምዕራብ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ‘የአፍሪካ ዓይን’ የተሰኘውን የአቡጃ ዋና መሥሪያ ቤቱን ይፋ አደረገ

ናይጄሪያ በቀጣናው ይበልጥ የጠነከረ ውህደት እና ኢንዱስትሪ ማስፋፋት እንዲኖር በዋና መሥሪያ ቤቱ ምርቃት ላይ አሳስባለች፡፡

አዲሱ ዋና መሥሪያ ቤት የሚከተሉትን ያካትታል፦

▪ ዘመናዊ የቢሮ ሕንፃዎች፣

▪ 800 ሰዎችን መያዝ የሚችል የጉባኤ ማዕከል፣

▪ የትርጉም ሥርዓት የተገጠመላቸው የስብሰባ አዳራሾች፣

▪ የስፖርት ማዘውተሪያ (ጂምናዚየም) እንዲሁም

▪ የኤግዚቢሽን ቦታዎች።

ፕሬዝዳንት ቲኑቡን በመወከል ማብራሪያ የሰጡት ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሸቲማ፤ ኢኮዋስ በሰላም፣ በትብብር እና በነፃ የሰዎች ዝውውር ረገድ ባሳየው መሻሻል በዓለም ላይ ካሉ እጅግ የተከበሩ ቀጣናዊ ተቋማት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ምክትል ፕሬዝዳንቱ ሲናገሩም፣ “ቀጣናዊ ውህደት ከእንግዲህ የኢኮኖሚ ግዴታ ብቻ ሊሆን አይችልም። ይልቁንም ለጋራ ደህንነታችን፣ ለፖለቲካዊ መረጋጋታችን፣ ለዘላቂ ልማታችን እና ለሕዝቦቻችን ደህንነት አጠቃላይ ማዕቀፍ ሆኗል” ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0