የታንዛኒያ ሆስፒታል ለካንሰር ታማሚዎች ተስፋን ለመመለስ የጡት መልሶ ማገንባት ፕሮግራም ጀመረ
19:20 03.07.2026 (የተሻሻለ: 19:24 03.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የታንዛኒያ ሆስፒታል ለካንሰር ታማሚዎች ተስፋን ለመመለስ የጡት መልሶ ማገንባት ፕሮግራም ጀመረ
በ2023/24 ብቻ ወደ 200 የሚጠጉ ታንዛኒያውያን ሴቶች የጡት መቆረጥ ቀዶ ሕክምና ያደረጉ ቢሆንም፤ ብዙዎቹ ግን የመልሶ ማገንባት አገልግሎት የማግኘት ዕድል የላቸውም ሲል ሙሂምቢሊ ብሔራዊ ሆስፒታል አዲሱን ተነሳሽነት ባበሰረበት ወቅት ገልጿል።
“የጡት ካንሰር በታንዛኒያ በሴቶች ላይ በቀዳሚነት የሚጠቀስ የካንሰር ዓይነት ሆኖ ቀጥሏል፤ ሆኖም ግን ብዙ ሕመምተኞች የጡት መቆረጥ ቀዶ ሕክምና ካደረጉ በኋላ መልሶ የማገንባት አገልግሎት አያገኙም” ሲሉ የፕላስቲክ እና መልሶ ማገንባት ቀዶ ጥገና ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ኢብራሂም ምኮማ ተናግረዋል።
ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
🟠 ሆስፒታሉ አንዱን ቀዶ ሕክምና በተሳካ ሁኔታ ያከናወነ ሲሆን በዚህ ሳምንት ደግሞ ለአራት ተጨማሪ ቀዶ ሕክምናዎች እየተዘጋጀ ይገኛል።
🟠 ምርመራ ከተደረገላቸው 18 ሕመምተኞች መካከል ስድስቱ ለቀዶ ሕክምናው ብቁ ሆነው ተገኝተዋል።
🟠 የቀዶ ሕክምና ሂደቱ ከራሱ ከሕመምተኛው ሌላ የሰውነት ክፍል የሚወሰድ ህብረ ህዋስን ይጠቀማል።
ከሆስፒታሉ ጋር በትብብር እየሠራ የሚገኘው የፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና ባለሙያ ዶ/ር ኤድዋርድ ሚራንዳ እንዳሉት፤ የጡት ካንሰር 10 በመቶ የሚሆኑ ሴቶችን በሕይወት ዘመናቸው የሚያጠቃ በመሆኑ ጡትን መልሶ ማገንባት የሕክምናው ወሳኝ አካል ያደርገዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X