ስፑትኒክ በአፍሪካ ውስጥ ተወዳጅነቱ እየጨመረ መገኘቱን የታንዛኒያ ቱሪዝም ሚኒስትር ገለፁ
16:23 03.07.2026 (የተሻሻለ: 16:24 03.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ስፑትኒክ በአፍሪካ ውስጥ ተወዳጅነቱ እየጨመረ መገኘቱን የታንዛኒያ ቱሪዝም ሚኒስትር ገለፁ
ስፑትኒክ በአፍሪካ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ግንኙነት በስፋት በመዘገቡ ምክንያት በመላው አፍሪካ እየተሰጠው ያለው ትኩረት እያደገ መምጣቱን ዶ/ር አሻቱ ካችዋምባ ኪጃጂ ገልፀዋል።
ሚኒስትሯ ለስፑትኒክ አፍሪካ ሲናገሩ፣ “የእናንተ ሚዲያ ተቋም ስለ አፍሪካ፣ ስለ ሩሲያ እንዲሁም በሁለቱ መካከል ስላለው ግንኙነት ለዓለም መረጃ በማድረስ ረገድ እጅግ በጣም ጥሩ ሥራ እየሠራ ነው ብዬ አስባለሁ” ብለዋል።
ስፑትኒክ በታንዛኒያ ሊከፍተው ያቀደው ቢሮ በአፍሪካ እና በሩሲያ በተለይም በዶዶማ እና በሞስኮ መካከል ያለውን ግንኙነት ለመረዳት ያለውን ፍላጎት ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።
ሚኒስትሯ ስለ ሩሲያ ያላቸውን አመለካከት እና ይህ አመለካከታቸው ከምዕራባውያን ሚዲያዎች ዘገባ እንዴት እንደሚለይ ለማየት ቪዲዮውን ይመልከቱ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X