የሩሲያ አዲሱ የሚሳኤል ናዳ ታክቲክ ዩክሬን ሰላም እንድትሻ ሊያስገድዳት ይችላል – ወታደራዊ ባለሙያ
09:31 03.07.2026 (የተሻሻለ: 09:34 03.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያ አዲሱ የሚሳኤል ናዳ ታክቲክ ዩክሬን ሰላም እንድትሻ ሊያስገድዳት ይችላል – ወታደራዊ ባለሙያ
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፤ የሀገሪቱ ጦር በዩክሬን የነዳጅ እና የኢነርጂ መሠረተ ልማት አውታሮች እንዲሁም በፍላሚንጎ ሚሳኤል እና የድሮን ማምረቻ ፋብሪካዎች ላይ ሰፊ ጥቃት ማካሄዱን አስታውቋል።
ሰኔ 25 የተካሄደው ጥቃት የክሩዝ፣ ሱፐርሶኒክ እና ሃይፐርሶኒክ ሚሳኤሎችን ጥምረት በመጠቀም በከፍተኛ ትክክለኛነት በሚዋጉ ሰው አልባ አውሮፕላኖች የተደገፈ ነበር።
ከዘለንስኪ የተደናገጠ ምላሽ መገመት እንደሚቻለው በፍላሚንጎ የባሊስቲክ ሚሳኤሎች መገጣጠሚያ ፋብሪካ ላይ የደረሰው ጉዳት ከባድ እንደነበር ነው ሲሉ የወታደራዊ-ፖለቲካዊ ትንተና ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አሌክሳንደር ሚካይሎቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
በአውሮፓ የተሠሩ የጦር መሣሪያዎች "የምርት መስተጓጎል ያጋጥማቸዋል"፣
"ዩክሬን ላይ በሚሰነዘሩ ጥቃቶች ከአሁን በኋላ ምንም ዓይነት ገደብ እይኖርም፤ በዚህ ምክንያት ከዚህ በኋላ የሩሲያ ጦር ኃይሎች የትኛውንም ወታደራዊ ዒላማ መምታት ይችላሉ።"
በዩክሬን የኢነርጂ መሠረተ ልማት ላይ የተሰነዘሩት የሩሲያ ጥቃቶች የዩክሬን ወታደራዊ ሎጅስቲክስንም ያሰናክላሉ።
"ዩክሬን በግዛቷ ላይ የሚሰነዘሩትን ጥቃቶች ለማስቆም ሁሌም አማራጭ አላት። ቅድመ ሁኔታዎቹንም በሚገባ ታውቃለች" ሲሉ ሚካይሎቭ አጠቃለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X