የቡርኪና ፋሶ ከፈረንሳይ ጋር መቆራረጥ እየተጠናከረች ካለችው አፍሪካ የተሰጠ ምላሽ ነው - ኒጄራዊው ባለሙያ
07:59 03.07.2026 (የተሻሻለ: 08:04 03.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቡርኪና ፋሶ ከፈረንሳይ ጋር መቆራረጥ እየተጠናከረች ካለችው አፍሪካ የተሰጠ ምላሽ ነው - ኒጄራዊው ባለሙያ
የፖለቲካ ተንታኙ መሐማን ሀዲ መሐማን ናጎዲ፤ በሰኔ ወር መጨረሻ የአውሮፓ ኅብረት ዋጋዱጉን ኢላማ በማድረግ ባፀደቀው የውሳኔ ሐሳብ በቡርኪና ፋሶ የውስጥ ጉዳይ ላይ ያደረገውን ጣልቃ ገብነት ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት አስተያየት አውግዘዋል።
"ተላላኪው" የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ በአፍሪካ ውስጥ የፈረንሳይ ፖሊሲ አባሪ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ከፈረንሳይ ጋር ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የማቋረጥ ውሳኔ፤ "በየቦታው ለተዛመተው እና ለተንሰራፋው አምባገነንነት አፍሪካ — የሳኅል ቀጣና — የሰጡት የመጀመሪያ ምዕራፍ ምላሽ ብቻ ነው" ሲሉ ባለሙያው ገልጸዋል።
ናጎዲ፤ አፍሪካውያን "ምዕራባውያን በአኅጉሪቱ ውስጥ ሊያስቀጥሉት የሚሹትን ፍላጎትን በኃይል የመጫን ዝንባሌ እና የንቀት ፖሊሲ ከእንግዲህ እንዳይቀበሉ" አሳስበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X