ከአዲስ አበባ ውጪ የመጀመሪያ የሆነው ከላይ ተሽከርካሪ ሕንጻ በቅርቡ በአርባ ምንጭ እንደሚመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ
19:19 02.07.2026 (የተሻሻለ: 19:24 02.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ከአዲስ አበባ ውጪ የመጀመሪያ የሆነው ከላይ ተሽከርካሪ ሕንጻ በቅርቡ በአርባ ምንጭ እንደሚመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ
ሕንጻው የስብሰባ፣ ኮንፈረንስና ኤግዚቢሽን ቱሪዝም አካል ሆኖ የተገነባ ግዙፍ ሬስቶራንት እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የፕሮጀክት አስደናቂ ገጽታዎች፦
🟠 በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ግዙፍ አዳራሽ ያካትታል፣
🟠 ሕንጻው የተሠራው ሐይቅ ውስጥ ነው፣
🟠 የሕንጻው የመጨረሻ ፎቅ ዘመናዊ ተሽከርካሪ ሬስቶራንት አለው፣
🟠 ከአርባ ምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ በ5 እና 6 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚገኝ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ አዲሱ ፕሮጀክት የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ቁጥር በመሳብ ግንባር ቀደም መዳረሻ ይሆናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት ያመነጨነው የፕሮጀክቱ ገላጭ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X