ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን የድንበር ንግድ ፕሮቶኮላቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመተግበር ተስማሙ
16:34 02.07.2026 (የተሻሻለ: 16:44 02.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን የድንበር ንግድ ፕሮቶኮላቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመተግበር ተስማሙ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ፤ ከደቡብ ሱዳን የፒቦር ልዩ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ ቦዮይ ጎላ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት ፕሮቶኮሉ የሁለቱን ሀገራት የድንበር ማኅበረሰብ ተጠቃሚነት ማዕከል ያደርገ እንደሆነ ገልጸዋል።
እንደ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር መረጃ ሁለቱ ኃላፊዎች ከታች በተዘረዘሩት ጉዳዮች ዙሪያም ተወያይተዋል፦
▪ ሕገ-ወጥ የድንበር ንግድን ስለመግታት፣
▪ መደበኛና ሕጋዊ የኢኮኖሚ አጋርነት ስለመፍጠር፣
▪ ስለድንበር ደኅንነት።
ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የድንበር ንግድ ፕሮቶኮሉን ወደ ትግበራ ለማሸጋግር ቁርጠኝነታቸውን በመግለጽ ውይይታቸውን እንዳጠናቀቁ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X