በ1994ቱ የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ወንጀል የተጠረጠ ግለሰብ ጀርመን ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋለ
15:00 02.07.2026 (የተሻሻለ: 15:04 02.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በ1994ቱ የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ወንጀል የተጠረጠ ግለሰብ ጀርመን ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋለ
የጀርመን ባለሥልጣናት በቱትሲዎች ላይ በተፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀል ተሳትፎ አለው ተብሎ የተጠረጠረና የጀርመን-ሩዋንዳ ዜግነት ያለውን ግለሰብ በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር አውለዋል።
ግለሰቡ በአምስት የተለያዩ አጋጣሚዎች የ25 ቱትሲዎችን ግድያ አዟል በሚል የተከሰሰ ሲሆን በአንዱ ግድያ ደግሞ ራሱ የአንድን ሰው ደረት በስለት በመውጋት በግንባር ቀደምትነት በወንጀሉ መሳተፉ ተገልጿል።
በሰሜን ምዕራብ ሩዋንዳ የአንድ ወረዳ መሪ ረዳት ሆኖ በሰራበት ወቅት፤ ሥልጣኑን ተጠቅሞ ግድያዎችን በመቀስቀስ፣ የሚገደሉ ሰዎችን ዝርዝር በማዘጋጀት እና በቱትሲ ተወላጆች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን በማስተባበር ተጠርጥሯል።
የጀርመን ዓቃቤ ሕግ ግለሰቡን በዘር ማጥፋት ተባባሪነት እና በበርካታ የነፍስ ማጥፋት ወንጀሎች ለመክሰስ የሚያስችል በቂ ማስረጃ መኖሩን አስታውቋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X