ሩሲያ የዩክሬንን ጦር ነዳጅ የሚያሳጣ አዲስ ስልት እየተከተለች ነው - ወታደራዊ ተንታኝ
10:06 02.07.2026 (የተሻሻለ: 10:14 02.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ የዩክሬንን ጦር ነዳጅ የሚያሳጣ አዲስ ስልት እየተከተለች ነው - ወታደራዊ ተንታኝ
ሩሲያ በምስራቃዊ እና መካከለኛው ዩክሬን ቢያንስ 25 የነዳጅ ማደያዎች እና በርካታ የነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት መፈጸሟን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የዩክሬን ጦር የአቅርቦት መስመሮች የሲቪል ተሽከርካሪዎችን እና መሠረተ ልማቶችን የሚጠቀም በመሆኑ የነዳጅ ማደያዎቹ ሕጋዊ የጥቃት ኢላማዎች ናቸው ሲሉ ወታደራዊ ተንታኙ አሌክሲ ሊዮንኮቭ ለስፑትኒክ ተናገረዋል።
▪ ጥቃቱ ከነዳጅ ማጣሪያ እስከ ነዳጅ ማደያ ጣቢያዎች ያለውን አጠቃላይ ሰንሰለት ያቋርጣል፣
▪ የነዳጅ እጥረት የዩክሬንን የወታደር ቅያሬ እና ተጨማሪ ኃይል የማንቀሳቀስ ሂደት ሊያሽመደምደው ይችላል፣
▪ የጦር መሣሪያ እና የጥይት አቅርቦት ሎጅስቲክ ላይም ከፍተኛ መስተጓጎል ይፈጥራል።
ሊዮንኮቭ አክለውም፤ “ስለ ሲቪሉ ሕዝብ ደህንነትማ፤ የዩክሬን ጁንታ ምንም ግድ የለውም። በጦር ግንባር ላይ ላሉት እንደማይራሩት ሁሉ፤ ከግንባር በስተጀርባ ላሉትም አይራሩላቸውም” ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X