የኔታንያሁ የጋዛ የማፈናቀል ዕቅድ እስራኤል የፍልስጤምን ይዞታ የመያዝ ዓላማ እንዳላት ያሳያል - ባለሙያ
09:04 02.07.2026 (የተሻሻለ: 09:14 02.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኔታንያሁ የጋዛ የማፈናቀል ዕቅድ እስራኤል የፍልስጤምን ይዞታ የመያዝ ዓላማ እንዳላት ያሳያል - ባለሙያ
እስራኤል ሶማሊላንድ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና ሊቢያ የጋዛ የፍልስጤም ስደተኞችን እንዲቀበሉ ጠይቃ፤ ሁሉም ሀገራት ሐሳቡን ውድቅ እንዳደረጉት ወይም ምንም ዓይነት ስምምነት አለመኖሩን እንዳስተባበሉ ተዘግቧል።
“ይህ እስራኤል በፍልስጤም ሕዝብ የተያዙትን እና የምትቆጣጠራቸውን ግዛቶች ለማስፋፋት የምትከተለው ፖሊሲ ነው" ሲሉ በአንካራ የፀጥታና የፖለቲካ ተንታኝ ሰሊም ኦዘርተም ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
ከጋዛ የሚደረግ ከፍተኛ የሕዝብ ፍልሰት “የሥልጣን ክፍተት” ሊፈጥር እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
እንዲሁም እስራኤል ግዛቱን ወደ ራሷ ማጠቃለሏ በአረብ መሪዎችና ዜጎች ዘንድ ፈጽሞ ተቀባይነት እንደማይኖረው ገልጸዋል።
ስደተኞችን መቀበል “የሥራ ስምሪት፣ የጤና እና የማኅበራዊ ዋስትና ችግሮች የሚጋፈጡ ሰዎችን እና አዳዲስ ባሕሎችን መቀበል ማለት ነው።”
ኦዘርተም አክለውም፤ “እስራኤል በጋዛ ወታደራዊ ጫና ባማድረስ፤ የቀጣናውን የሥነ-ሕዝብ ስብጥር ለመቀየር አማራጭ መፍትሔዎችን እየፈለገች ነው” ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X