ፈረንሳይ በቡርኪና ፋሶ ድንገተኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የማቋረጥ ውሳኔ ተደናግጣለች ተባለ
18:02 01.07.2026 (የተሻሻለ: 18:04 01.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፈረንሳይ በቡርኪና ፋሶ ድንገተኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የማቋረጥ ውሳኔ ተደናግጣለች ተባለ
የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት መሻከሩን ብታወቅም፤ ዋጋዱጉ ለፈረንሳይ ኤምባሲ መዝጊያ የአንድ ሳምንት ጊዜ ብቻ መስጠቷ ለፓሪስ ያልተጠበቀ ውሳኔ እደሆነባት አንድ የፈረንሳይ ጋዜጣ አስነብቧል።
ፈረንሳይም በተመሳሳይ በሀገሯ የሚገኙ የቡርኪና ፋሶ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖችን ለመዝጋት ማቀዷን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ይህ ድንገተኛ ፍቺ የቪዛ አገልግሎትን በማቋረጡ በቡርኪና ፋሶ የሚኖሩ 2 ሺህ 500 ገደማ የፈረንሳይ ዜጎች ለቆንስላ አገልግሎት የሌሎች የአውሮፓ ኅብረት ሀገራት ኤምባሲዎችን እንዲጠቀሙ ማስገደዱን መገናኛ ብዙኃን አንድ የፈረንሳይ ዲፕሎማትን ዋቢ አድርገው አመልክተዋል።
ቡርኪና ፋሶ ፈረንሳይን በሽብርተኝነት እና ኒዮ-ኮሎኒያሊዝም ወንጅላ ሰኔ 19 ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን በይፋ አቋርጣለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X