ተመድ በቡርኪና ፋሶ የሚገኘውን የሰብዓዊ መብቶች ቢሮ ሊዘጋ ነው
17:44 01.07.2026 (የተሻሻለ: 17:54 01.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ተመድ በቡርኪና ፋሶ የሚገኘውን የሰብዓዊ መብቶች ቢሮ ሊዘጋ ነው
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የረጅም ጊዜ እገዳ ሲያጋጥም የሚሠራውን አንቀጽ ተግባራዊ እንደሚያደርግ የተመድ ተጠባባቂ አስተባባሪ ሞሪስ አዞናንክፖ ከቡርኪና ፋሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካራሞኮ ዣን ማሪ ትራኦሬ ጋር ባደረጉት ስብሰባ ተናግረዋል።
ዳራ፡- የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ፤ ቡርኪና ፋሶ የሲቪክ ምህዳሩን እያጠበበች ነው በማለት መክሰሳቸውን ተከትሎ ዋጋዱጉ በሚያዝያ ወር የጽሕፈት ቤቱን እንቅስቃሴዎች አግዳለች።
ቢሮውን በስድስት ወራት ውስጥ የመዝጋት ሂደት የሚያስተባብር ብሔራዊ ተጠሪ እንደሚሰየም የቡርኪና ፋሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ቡርኪናፋሶ፤ ፓሪስ የመከባበር እና በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ያለመግባት መርሆዎችን በመጣሷ ከፈረንሳይ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማቋረጧን ሰኔ 19 ቀን ማስታወቋ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X