ዩክሬን እና ፈረንሳይ በአፍሪካ ዓላማቸውን ለማሳካት አሸባሪዎችን እየተጠቀሙ ነው - የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት

© telegram sputnik_ethiopiaዩክሬን እና ፈረንሳይ በአፍሪካ ዓላማቸውን ለማሳካት አሸባሪዎችን እየተጠቀሙ ነው - የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት
ዩክሬን እና ፈረንሳይ በአፍሪካ ዓላማቸውን ለማሳካት አሸባሪዎችን እየተጠቀሙ ነው - የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.07.2026
ሰብስክራይብ

ዩክሬን እና ፈረንሳይ በአፍሪካ ዓላማቸውን ለማሳካት አሸባሪዎችን እየተጠቀሙ ነው - የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት

​ ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣ የአውሮፓ ሀገራት ጥቅማቸውን ለማስከበር፤ አሸባሪ ቡድኖችን እንደሚጠቀሙና መረጃ እንደሚያቀብሏቸውም የሩሲያ ደኅንነት ምክር ቤት ምክትል ፀሐፊ አሌክሳንደር ቬኔዲክቶቭ ለመገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።

​ ዩክሬን በአፍሪካ አኀጉር ጭምር ይህንን ድርጊት “በንቃት እያከናወነች” እንደምትገኝና በዚህ ረገድም “ብቻዋን እንዳልሆነች” የጠቀሱት ቬኔዲክቶቭ፤ በአሁኑ ወቅት የዩክሬን ወታደራዊ አማካሪዎች በአፍሪካ የነቃ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሆነ አረጋግጠዋል።

​“ፈረንሳይ እንዲህ ካሉ ድርጊቶች ወደኋላ እንደማትል እናውቃለን፤ ቀደም ሲል በቅኝ ግዛት ሥር በነበሩ ክፍሎች አዲስ የቅኝ አገዛዝ ቁጥጥር ለመመስረት የሚሹ በርካታ የአውሮፓ ሀገራትም በተመሳሳይ ይህንን መንገድ ይጠቀማሉ” ብለዋል።

 

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0