የቡርኪና ፋሶ እና ፈረንሳይ ፍቺ ያበቃለት ጉዳይ ነው - የኅብረተሰብ አጥኚ

ሰብስክራይብ
የቡርኪና ፋሶ እና ፈረንሳይ ፍቺ ያበቃለት ጉዳይ ነው - የኅብረተሰብ አጥኚ

ኡጋዱጉ ከፓሪስ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማቋረጥ ያስተላለፈችው ውሳኔ፤ በተግባር፣ በአድራጎት እና በሃሳብ ቀድሞውኑ ሥራ ላይ የዋለውን መለያየት ይፋዊ ያደረገ ብቻ መሆኑን የኅብረተሰብ አጥኚው እና የቡርኪና ፋሶ ንቁ ዜጎች ንቅናቄ አባል የሆኑት ፋራጋ ኔብኖማ ባሲል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።


ውሳኔው "አቋማችንን እያረጋገጥን መሆናችንን እና አሁን ካለው የፈረንሳይ መንግሥት ጋር ለመቀጠል ፍላጎት እንደሌለን ለመላው ዓለም ያሳያል" ሲሉ ባለሙያው አክለዋል።


ቡርኪና ፋሶ አሁን በትሩን ለሌሎቹ የሳኅል ጥምረት ሀገራት እያስተላለፈች ነው ያሉት ባለሙያው፤ እነርሱም ተመሳሳይ ውሳኔ ለመውሰድ አይዘገዩም ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0