የሱዳን ታጣቂዎች በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ከተማ የሰነዘሩት ጥቃት በሰው ሠራሽ አስተውህሎት ፕሮፓጋንዳ የተቀነባበረ ነበር - በባንጉዊ የሩሲያ የባሕል ማዕከል ኃላፊ
20:10 30.06.2026 (የተሻሻለ: 20:14 30.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሱዳን ታጣቂዎች በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ከተማ የሰነዘሩት ጥቃት በሰው ሠራሽ አስተውህሎት ፕሮፓጋንዳ የተቀነባበረ ነበር - በባንጉዊ የሩሲያ የባሕል ማዕከል ኃላፊ
በአም ዳፎክ ከተማ የተሰነዘረው ጥቃት በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የተቀነባበረ ፕሮፓጋንዳን በሚጠቀም አዲስ የተቋቋመ የታጣቂዎች ቡድን የተፈጸመ መሆኑን በባንግዊ የሩሲያ ማዕከል ዳይሬክተር ዲሚትሪ ሲቲ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ይህ ንቅናቄ በስደት ላይ በሚገኙት የቀድሞው የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የፓርላማ አባል ካሪም መካሱዋ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደረግለትና ምናልባትም ከፈረንሳይ ታክቲካዊ ምክር ሳይለገሰው እንዳልቀረ የተጠቆመ ሲሆን ግልጽ የፖለቲካ አጀንዳ ከማንገብ ይልቅ ፍርሃት የመዝራትና ትኩረት የመሳብ ዓላማ እንዳለው ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
በሩሲያ ስፔሻሊስቶች ከተመራው የአየር ድብደባ በኋላ ታጣቂዎቹ በጅምላ ወደ ሱዳን ድንበር መሸሻቸውን ሲቲ ጠቁመዋል።
ዳይሬክተሩ በአም ዳፎክ ያለው ሁኔታ አሁን የተረጋጋ መሆኑን ያረጋገጡ ሲሆን ተጨማሪ ድንበር ተሻጋሪ ጥቃቶችን ለመከላከል የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ወታደሮች እና የሩሲያ ወታደራዊ አሠልጣኞች በአካባቢው ቁጥጥር እያጠናከሩ እና የዋና ዋና መስመሮችን ደህንነት እያስጠበቁ መሆናቸውን አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X