የሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በዓለም አቀፍ የፓርላማ ቀን ለኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ደቡብ አፍሪካ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
19:27 30.06.2026 (የተሻሻለ: 19:34 30.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በዓለም አቀፍ የፓርላማ ቀን ለኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ደቡብ አፍሪካ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ቫለንቲና ማትቪየንኮ ለብሪክስ አባል ሀገራት ፓርላማዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቱን እንደላኩ የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ማትቪየንኮ ለኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት፤ የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ሕግ አውጪዎች በሁለትዮሽም ሆነ በዓለም አቀፍ የፓርላማ ድርጅቶች ማዕቀፍ ውስጥ ትብብራቸውን እንደሚቀጥሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።
"የሩሲያ ፌዴሬሽን ሴናተሮች ከደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፓርላማ የክልል ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት ጋር ያላቸውን ፍሬያማ ትብብር በብሪክስ፣ በቡድን 20 እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ማዕቀፋት ውስጥ ለማጠናከር ይሻሉ" ሲሉ ለደቡብ አፍሪካ ፓርላማ አባላት በላኩት መልዕክት ተናግረዋል።
ሩሲያ ከግብፅ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ አጋርነት እያጠናከረች መሆኑንም አክለዋል።
በ2018 በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ የፀደቀው ዓለም አቀፍ የፓርላማ ቀን፤ እ.አ.አ በየዓመቱ ሰኔ 30 ቀን ይከበራል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X