ሩሲያ እና ሩዋንዳ አነስተኛ ሞዱላር የኒውክሌር ሪአክተሮችን ለማልማት የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸውን ሮሳቶም አስታወቀ

ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ሩዋንዳ አነስተኛ ሞዱላር የኒውክሌር ሪአክተሮችን ለማልማት የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸውን ሮሳቶም አስታወቀ

ሮሳቶም እና ሩዋንዳ የመጀመሪያውን የጋራ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ በሞስኮ በማካሄድ ከማዕቀፍ ስምምነቶች ወደ ተጨባጭ ተግባር መሸጋገራቸውን የሩሲያ ኮርፖሬሽን አስታውቋል።

በውይይቱ ወቅት ሁለቱም የዘርፉን የትብብር ሂደት ገምግመዋል፦

▪ የሩዋንዳን የኒውክሌር ኃይል ፕሮግራም፣

▪ የኒውክሌር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ማዕከል ማቋቋም፣

▪ የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ልማት፡፡

ሮሳቶም ባጋራው መግለጫ መሠረት፤ ስብሰባው በሩዋንዳ አነስተኛ ሞዱላር ሪአክተሮች ላይ የተመሠረቱ የኒውክሌር  ኃይል ማመንጫዎችን ለመገንባት የሚያስችል ፕሮቶኮል በመፈራረም ተጠናቋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0