ሩሲያ እና ሩዋንዳ አነስተኛ ሞዱላር የኒውክሌር ሪአክተሮችን ለማልማት የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸውን ሮሳቶም አስታወቀ
17:26 30.06.2026 (የተሻሻለ: 17:34 30.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ እና ሩዋንዳ አነስተኛ ሞዱላር የኒውክሌር ሪአክተሮችን ለማልማት የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸውን ሮሳቶም አስታወቀ
ሮሳቶም እና ሩዋንዳ የመጀመሪያውን የጋራ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ በሞስኮ በማካሄድ ከማዕቀፍ ስምምነቶች ወደ ተጨባጭ ተግባር መሸጋገራቸውን የሩሲያ ኮርፖሬሽን አስታውቋል።
በውይይቱ ወቅት ሁለቱም የዘርፉን የትብብር ሂደት ገምግመዋል፦
▪ የሩዋንዳን የኒውክሌር ኃይል ፕሮግራም፣
▪ የኒውክሌር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ማዕከል ማቋቋም፣
▪ የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ልማት፡፡
ሮሳቶም ባጋራው መግለጫ መሠረት፤ ስብሰባው በሩዋንዳ አነስተኛ ሞዱላር ሪአክተሮች ላይ የተመሠረቱ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫዎችን ለመገንባት የሚያስችል ፕሮቶኮል በመፈራረም ተጠናቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X