የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር የሲሸልስ ጉብኝት 19 ስምምነቶች፣ አዳዲስ ተነሳሽነቶች እና የባሕር ደህንነት ትብብር አፈራ
16:29 30.06.2026 (የተሻሻለ: 16:34 30.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር የሲሸልስ ጉብኝት 19 ስምምነቶች፣ አዳዲስ ተነሳሽነቶች እና የባሕር ደህንነት ትብብር አፈራ
በሲሸልስ 50ኛ ዓመት ብሔራዊ ቀን በክብር እንግድነት የተገኙት ናሬንድራ ሞዲ፤ ከፕሬዚዳንት ፓትሪክ ሄርሚኒ ጋር በጤና፣ በትምህርት፣ በአቅም ግንባታ እና በባሕር ደህንነት ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።
የጉብኝቱ ዋና ዋና ፍሬዎች የሚከተሉት ናቸው፦
▪ 6 የባህር ላይ ጀልባዎች እና 16 አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች ለሲሸልስ መከላከያ ኃይል ተበርክተዋል፣
▪ 500 ቶን ሩዝ እና 8 ሺህ 500 ቶን ሲሚንቶ ድጋፍ ተደርጓል፣
▪ ሲሸልስ የአደጋ መቋቋም መሠረተ-ልማት ጥምረትን ተቀላቅላለች።
በተጨማሪም የሚከተሉትን ዘርፎች የሚያካትቱ 9 የመግባቢያ ስምምነቶች ተፈራርመዋል፦
▪የጤና እንክብካቤ፣
▪የዲጂታል መሠረተ-ልማት ግንባታ፣
▪ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በጋራ መከላከል፣
▪የባሕር ጉዞ እና አሰሳ፣
▪የባሕር ንግድ፣
▪የሕዋ ምርምር ትብብር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ለሲሸልስ ብሔራዊ ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር፤ የአየር ንብረት ለውጥ እርምጃዎች "ፍትሐዊነትን፣ ኃላፊነትን እና እኩልነትን የተከተሉ" መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X