የስፑትኒክ ራዲዮ ጋዜጠኛ አሊ ቻጋታይ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት ሳቢያ በቱርክ ለእስር ተዳረገ

© telegram sputnik_ethiopiaየስፑትኒክ ራዲዮ ጋዜጠኛ አሊ ቻጋታይ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት ሳቢያ በቱርክ ለእስር ተዳረገ
የስፑትኒክ ራዲዮ ጋዜጠኛ አሊ ቻጋታይ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት ሳቢያ በቱርክ ለእስር ተዳረገ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.06.2026
ሰብስክራይብ

የስፑትኒክ ራዲዮ ጋዜጠኛ አሊ ቻጋታይ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት ሳቢያ በቱርክ ለእስር ተዳረገ

​የኢስታንቡል ዋና ዓቃቤ ሕግ ቢሮ የስፑትኒክ ራዲዮ የጠዋት ፕሮግራም አዘጋጅ አሊ ቻጋታይ በግል የኤክስ ገፁ ባጋራው መረጃ ምክንያት የወንጀል ምርመራ ከፍቶበታል።

​ ቻጋታይ ከፍተኛ ትኩረት የሳበውን የኢስታንቡል ማዘጋጃ ቤት የባሕልና ቱሪዝም አገልግሎት ሰጪ ተቋም ምክትል ኃላፊ ኤርሃን ካራኣልን ዕገታ በተመለከተ አስተያየት መስጠቱን ተከትሎ ነው ሊታሰር የቻለው።

​ አጋቾቹ ካራኣልን ሰኔ 10 ቀን ከቤታቸው መግቢያ አፍነው ከወሰዱ በኋላ ከ300 እስከ 500 ኪሎ ግራም ወርቅ ጠይቀው ነበር። ይሁን እንጂ ከ33 ሰዓታት በኋላ ፖሊስ ባካሄደው ኦፕሬሽን ነፃ ወጥተዋል።

​ የኢስታንቡል ዋና ዓቃቤ ሕግ ቢሮ ጋዜጠኛው "ሕግ አስከባሪ አካላትን የሚቃወሙ" መልዕክቶች አሠራጭቷል በማለት ምርመራ ጀምሯል። በመቀጠል ፍርድ ቤት በጋዜጠኛው ላይ የእስር ትዕዛዝ አውጥቷል።

​ አሊ ቻጋታይ እ.ኤ.አ ከ2020 ጀምሮ በስፑትኒክ ራዲዮ ዕለታዊ ፕሮግራም የሚያቀርብ ታዋቂ የቱርክ ጋዜጠኛ ነው።

​ ቀደም ሲል "ሁሪያት" እና "ራዲካል" በተባሉ ጋዜጦች እንዲሁም "ሃበርቱርክ" በተሰኘው የቴሌቪዥን ጣቢያ የዜና ክፍል ኃላፊ በመሆን አገልግሏል።

​ በኢስታንቡል የሚገኘው የስፑትኒክ ራዲዮ የዜና ክፍል ቻጋታይን የሚደግፉ በርካታ መልዕክቶች የደረሱት ሲሆን የፕሮግራሙ አድማጮች ጋዜጠኛው በአስቸኳይ እንዲፈታ እየጠየቁ ይገኛሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0