ቡርኪና ፋሶ የቀጣናው የኤቪዬሽን ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ

ቡርኪና ፋሶ የቀጣናው የኤቪዬሽን ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ
ሀገሪቱ በአየር ትራፊክ ረገድ ጠንካራ ዕድገት እያሳየች እንደሆነና በአየር መንገድ ነዳጅ አቅርቦትም ተወዳዳሪ ብልጫ እንዳላት የቡሪኪና ፋሶ ኤርፖርቶች ባለሥልጣን ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።
ይህ ዕድገት ቡርኪና ፋሶን በምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ ከሚገኙ ዋና ዋና የኤቪዬሽን እና የሎጂስቲክ ማዕከላት አንዷ ሊያደርጋት እንደሚችል ሪፖርቱ ጠቁሟል።
ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 በኡጋዱጉ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የተሳፋሪዎች ፍሰት እ.ኤ.አ ከ2016 እስከ 2025 ባሉት ከአሥር ዓመታት ውስጥ ከ51 በመቶ በላይ ጭማሪ አሳይቷል።
🟠 የቀጣናዊ በረራ ትስስሮች የ52 በመቶ ተሳፋሪዎችን ድርሻ የሚይዙ ሲሆን የትራንዚት ትራፊክ ደግሞ ከጠቅላላው 30 በመቶ ይሸፍናል።
🟠 የሀገሪቱ አየር ማረፊያዎች እ.ኤ.አ በ2025 ከ8 ሺህ 680 ቶን በላይ ጭነት አስተናግደዋል።
ሀገሪቱ መሠረተ ልማት ላይ መጠነ ሰፊ ኢንቨስትመንት እያደረገች ትገኛለች፦
🟠 የኡጋዱጉ እና የቦቦ-ዲዩላሶ አየር ማረፊያዎቹን ማዘመን፣
🟠 የ "ፋዳ ንጉርማ"፣ "ዶሪ"፣ "ጋዋ" እና "ዋሂጉያ" አየር ማረፊያዎችን መልሶ ማልማት፣
🟠 የነፃ የንግድ ቀጣናዎች፣ የልዩ የኢኮኖሚ ቀጣናዎች፣ የጭነት ማዕከላት እንዲሁም የኤቪዬሽን ሥልጠና አካዳሚ ግንባታ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X