ቡርኪና ፋሶ የቀጣናው የኤቪዬሽን ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ

© telegram sputnik_ethiopiaቡርኪና ፋሶ የቀጣናው የኤቪዬሽን ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ
ቡርኪና ፋሶ የቀጣናው የኤቪዬሽን ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.06.2026
ሰብስክራይብ

ቡርኪና ፋሶ የቀጣናው የኤቪዬሽን ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ

​ ሀገሪቱ በአየር ትራፊክ ረገድ ጠንካራ ዕድገት እያሳየች እንደሆነና በአየር መንገድ ነዳጅ አቅርቦትም ተወዳዳሪ ብልጫ እንዳላት የቡሪኪና ፋሶ ኤርፖርቶች ባለሥልጣን ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

​ይህ ዕድገት ቡርኪና ፋሶን በምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ ከሚገኙ ዋና ዋና የኤቪዬሽን እና የሎጂስቲክ ማዕከላት አንዷ ሊያደርጋት እንደሚችል ሪፖርቱ ጠቁሟል።

ዋና ዋና ነጥቦች፦

​🟠 በኡጋዱጉ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የተሳፋሪዎች ፍሰት እ.ኤ.አ ከ2016 እስከ 2025 ባሉት ከአሥር ዓመታት ውስጥ ከ51 በመቶ በላይ ጭማሪ አሳይቷል።

​🟠 የቀጣናዊ በረራ ትስስሮች የ52 በመቶ ተሳፋሪዎችን ድርሻ የሚይዙ ሲሆን የትራንዚት ትራፊክ ደግሞ ከጠቅላላው 30 በመቶ ይሸፍናል።

​🟠 የሀገሪቱ አየር ማረፊያዎች እ.ኤ.አ በ2025 ከ8 ሺህ 680 ቶን በላይ ጭነት አስተናግደዋል።

ሀገሪቱ መሠረተ ልማት ላይ መጠነ ሰፊ ኢንቨስትመንት እያደረገች ትገኛለች፦

​🟠 የኡጋዱጉ እና የቦቦ-ዲዩላሶ አየር ማረፊያዎቹን ማዘመን፣

​🟠 የ "ፋዳ ንጉርማ"፣ "ዶሪ"፣ "ጋዋ" እና "ዋሂጉያ" አየር ማረፊያዎችን መልሶ ማልማት፣

​🟠 የነፃ የንግድ ቀጣናዎች፣ የልዩ የኢኮኖሚ ቀጣናዎች፣ የጭነት ማዕከላት እንዲሁም የኤቪዬሽን ሥልጠና አካዳሚ ግንባታ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0