ኢትዮጵያ በቻይናው የብሪክስ መድረክ አካታች የዲጂታል ትብብር እንዲኖር ጥሪ አቀረበች

© telegram sputnik_ethiopiaኢትዮጵያ በቻይናው የብሪክስ መድረክ አካታች የዲጂታል ትብብር እንዲኖር ጥሪ አቀረበች
ኢትዮጵያ በቻይናው የብሪክስ መድረክ አካታች የዲጂታል ትብብር እንዲኖር ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.06.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ በቻይናው የብሪክስ መድረክ አካታች የዲጂታል ትብብር እንዲኖር ጥሪ አቀረበች

በቻይና ኡሩምቺ እየተካሄደ ከሚገኘው 9ኛው የቻይና-ዩራሺያ ኤክስፖ ጎን ለጎን፣ “የብሪክስ ዲጂታል ኢንዱስትሪ ሥነ-ምህዳር የትብብር መረብ” ይፋ ሆኗል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተሳተፉት በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል መልዕክተኛ አዚዛ ገለታ (ዶ/ር)፤ ፍትሐዊና አካታች የዲጂታል ሽግግር አስፈላጊነትን አጉልተው አንስተዋል።

በኢትዮጵያ እየተመዘገቡ ያሉ የዲጂታል ዕድገቶች፣ በተለይም የዲጂታል ሕዝባዊ አገልግሎቶች፣ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት እና በቴሌብር አማካኝነት እየተስፋፋ ያለው የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በመድረኩ ተብራርተዋል።

ዶ/ር አዚዛ፣ የቴክኖሎጂ፣ የዲጂታል መሠረተ ልማት እና የኢንቨስትመንት እጥረት ለደቡባዊ ዓለም ሀገራት ዋነኛ ተግዳሮት መሆኑ ጠቅሰዋል።

የብሪክስ አባል ሀገራት በዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታ፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት አስተዳደር እና በዲጂታል ክህሎት ማሳደግ ዙሪያ ጠንካራ ጥምረት እንዲፈጥሩ ኢትዮጵያ ጥሪ አቅርባለች።

ኢትዮጵያ ሁሉንም ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት ከብሪክስ አጋሮቿ ጋር በቁርጠኝነት እንደምትሠራ ምክትል ዳይሬክተሯ በድጋሚ አረጋግጠዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
ኢትዮጵያ በቻይናው የብሪክስ መድረክ አካታች የዲጂታል ትብብር እንዲኖር ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ
1/3
© telegram sputnik_ethiopia
ኢትዮጵያ በቻይናው የብሪክስ መድረክ አካታች የዲጂታል ትብብር እንዲኖር ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ
2/3
© telegram sputnik_ethiopia
ኢትዮጵያ በቻይናው የብሪክስ መድረክ አካታች የዲጂታል ትብብር እንዲኖር ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ
3/3
1/3
2/3
3/3
አዳዲስ ዜናዎች
0