ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በድርብ መስፈርቶቹ ምክንያት የዕምነት ቀውስ ገጥሞታል - ሊባኖሳዊ የሕግ ፕሮፌሰር
12:55 27.06.2026 (የተሻሻለ: 13:04 27.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በድርብ መስፈርቶቹ ምክንያት የዕምነት ቀውስ ገጥሞታል - ሊባኖሳዊ የሕግ ፕሮፌሰር
አሁን ያለው ዓለም አቀፋዊ ሥርዓት በፍርድ ቤቱ ነፃነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩንና የተመሠረተበትን መሠረታዊ ዓላማ ማዳከሙን በሊባኖስ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ሕግ ፕሮፌሰር ሐሰን ጁኒ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
“ፍትሕን ለማስፈን በፍርድ ቤቱ መዋቅር እና አሠራር ላይ ጥልቅ ማሻሻያዎችን ማድረግ ያስፈልጋል” ሲሉ የተከራከሩት ፕሮፌሰሩ፤ ፍርድ ቤቱ ትኩረቱን በአብዛኛው አውሮፓውያን ባልሆኑ ሀገራት፣ በተለይም በአፍሪካ ሀገራት እና በሩሲያ ላይ ማድረጉን ጠቁመዋል።
ሩሲያ ፍርድ ቤቱ እንዲፈርስ ስላቀረበችው ጥሪ አስተያየታቸውን የሰጡት ጁኒ፤ እርምጃው የሞስኮን የአሁኑን ሥርዓት ውድቅ ማድረግ የሚያንጸባርቅበት የፖለቲካ ገጽታ እንዳለው ሁሉ፤ ሩሲያ የሮም ደንብ ፈራሚ አካል ባለመሆኗም ሕጋዊ ገጽታ እንዳለው አብራርተዋል።
ሩሲያ የጦር ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ ይበልጥ ፍትሐዊ በሆነ መንገድ የሚያረጋግጥ አማራጭ ዓለም አቀፋዊ ማዕቀፍ እንዲኖር እየገፋፋች ነው ሲሉም አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X