አፍሪካ የኒውክሌር እውቀትን መረዳት አለባት ማብለያዎችን በግዢ ማስገባት ብቻ በቂ አይደለም - የናይጄሪያው የወጣቶች መሪ

ሰብስክራይብ

አፍሪካ የኒውክሌር እውቀትን መረዳት አለባት ማብለያዎችን በግዢ ማስገባት ብቻ በቂ አይደለም - የናይጄሪያው የወጣቶች መሪ

ሩሲያ ከአፍሪካ የመጡ ተማሪዎችን በስኬት እያሠለጠነች ቢሆንም፤ ትኩረቱ ግን አሁንም በአብዛኛው በንድፈ-ሐሳብ ላይ ብቻ የተገደበ መሆኑን የ‘አፍሪካን ያንግ ጄነሬሽን ኢን ኒውክሌር’ ፕሬዝዳንት አቡበከር ሳዲቅ አሊዩ ከኦብኒንስክ ኤንኢደብሊው 2026 4ኛው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ኒውክሌር ፎረም ጎን ለጎን ለስፑትኒክ ተናግሯል።

በንድፈ-ሐሳብ እና በተግባራዊ ዓለም መካከል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ የልምምድ ፣ የሕብረት እና የሥልጠና መንገዶችን መፍጠር ያስፈልጋል ሲሉ አጽንኦት ሰጥቷል።

በተጨማሪም አሊዩ በአኅጉሪቱ የኒውክሌር ተነሳሽነቶችን ወደ ተግባር ለመለወጥ ፋይናንስ ዋነኛ ፈተና መሆኑን ጠቅሶ፤ የአፍሪካ ልማት ባንኮች መሰል ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ ወደፊት ይመጣሉ የሚል ተስፋውን ገልጿል።

‍  ሰኔ 19 በሞስኮ አቅራቢያ በምትገኘው ታዋቂዋ የሩሲያ የሳይንስ ከተማ ኦብኒንስክ ውስጥ፤ የዓለም የመጀመሪያው የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ የጀመረበት 72ኛ ዓመት መታሰቢያ ነው።

ℹ  ዓርብ ዕለት የተካሄደው የኦብኒንስክ ኤንኢደብሊው ፎረም፤ ወጣቶች የኒውክሌር ኢንዱስትሪውን እንዴት እየለወጡት እንደሆነ እና ምን ዓይነት የጋራ ፕሮጀክቶች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ ለመማር ከ70 ሀገራት የተወጣጡ ከ500 በላይ ወጣቶችን እና 10 ልዑካንን በአንድ ላይ አሳታፏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0