የአፍሪካ ሕብረት ቬንዙዌላ ላይ የደረሰውን የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከትሎ አጋርነቱን ገለፀ

ሰብስክራይብ

የአፍሪካ ሕብረት ቬንዙዌላ ላይ የደረሰውን የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከትሎ አጋርነቱን ገለፀ

የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ ሀገሪቱን የመታውን ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከትሎ ለተጎጂዎች ቤተሰቦች የተሰማቸውን ልባዊ መፅናናት የገለጹ ሲሆን፤ ለቆሰሉትም ፈጣን ማገገምን መመኘታቸውን ይፋዊ መግለጫው ጠቁሟል።

ሊቀመንበሩ የተጎዱ ማኅበረሰቦችን ለመርዳት ሳይታክቱ ለሚሠሩ የአስቸኳይ ጊዜ ነፍስ አድን ቡድኖች እና ሠራተኞችም አድናቆታቸውን ገልፀዋል።

ዩሱፍ “አሁን ላይ እየተደረጉ ያሉ የዕርዳታ፣ የማገገሚያ እና መልሶ ግንባታ ጥረቶች፤ የተጎዱ ማኅበረሰቦች ይህንን አሳዛኝ ክስተት በተቻለ ፍጥነት እንዲያሸንፉ ያስችላቸዋል” የሚል ተስፋ እንዳላቸው አያይዘው ጠቅሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0