“ሁሉም ግድግዳዎች መፍረስ አለባቸው” - የካራካስ ነዋሪ የመሬት መንቀጥቀጡን አስከፊ ውድመት ያስታውሳሉ

ሰብስክራይብ

“ሁሉም ግድግዳዎች መፍረስ አለባቸው” - የካራካስ ነዋሪ የመሬት መንቀጥቀጡን አስከፊ ውድመት ያስታውሳሉ

በቬንዙዌላው አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አፓርታማዋ የፈረሰባት የካራካስ ነዋሪዋ ኤሪካ ሳንቼዝ ታሪኳን ለስፑትኒክ አጋርታለች።

ሳንቼዝ ሲያብራሩ “እኔ የምኖርበት ሕንፃ በከፍተኛ ሁኔታ ተመትቷል፤ የመጀመሪያው ፎቅ የከፋ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፣ በመቀጠል ሁለተኛው ፎቅ፣ ሦስተኛው ፎቅ በጥቂቱ፣ ከአራተኛው ፎቅ በላይ ግን ምንም አልሆነም” ያሉ ሲሆን፣ አንድ መሐንዲስ መጥቶ በመጀመሪያው ፎቅ ላይ የሚገኘው የአፓርታማዋ ግድግዳዎች በሙሉ መፍረስ እንዳለባቸው እንደመከራት ጠቁመዋል።

ቬንዙዌላ በ40 ሰከንዶች ልዩነት ውስጥ ብቻ 7.2 እና 7.5 በሬክተር ስኬል የሚለኩ ሁለት ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች አስተናግዳለች። ይህ አደጋ ቢያንስ የ188 ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈ እና ከ1,500 በላይ ሰዎችን ያቆሰለ ሲሆን፤ የአስቸኳይ ጊዜ ነፍስ አድን ቡድኖች በፍርስራሾች ውስጥ በሕይወት የተረፉ ሰዎችን የመፈለግ ሥራቸውን ቀጥለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0