የሩሲያ ባንዲራ በመታገዱ ምክንያት የሮማንያ ጂምናስቲክ ፌዴሬሽን ቅጣት ሊጣልበት ይገባል - የምክር ቤት አባል

© telegram sputnik_ethiopiaየሩሲያ ባንዲራ በመታገዱ ምክንያት የሮማንያ ጂምናስቲክ ፌዴሬሽን ቅጣት ሊጣልበት ይገባል - የምክር ቤት አባል
የሩሲያ ባንዲራ በመታገዱ ምክንያት የሮማንያ ጂምናስቲክ ፌዴሬሽን ቅጣት ሊጣልበት ይገባል - የምክር ቤት አባል - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.06.2026
ሰብስክራይብ

የሩሲያ ባንዲራ በመታገዱ ምክንያት የሮማንያ ጂምናስቲክ ፌዴሬሽን ቅጣት ሊጣልበት ይገባል - የምክር ቤት አባል

ሁለት ጊዜ የኦሊምፒክ የፍጥነት ስኬቲንግ ሻምፒዮን እና የሩሲያ ስቴት ዱማ (የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት) ምክትል አባል የሆኑት ስቬትላና ዡሮቫ፤ የስፖርት ፌዴሬሽኖች የሩሲያ ስፖርተኞችን ከውድድሮች ለማግለል እንደ ብሔራዊ ምልክቶችን ማገድ ያሉ መሰሪ ስልቶችን እየተጠቀሙ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሩሲያ ብሔራዊ ኩራቷን በእጅጉ እንደምታከብር ያስገነዘቡት ዡሮቫ፤ ለሁሉም ተወዳዳሪዎች እኩል እና ፍትሐዊ ሁኔታዎችን የማመቻቸት ኃላፊነት የውድድሩ አስተናጋጅ ሀገር ነው ሲሉ አክለዋል።

ዡሮቫ ሲቀጥሉም “በሌላ በኩል ግን እኛ ራሳችንን አግልለን እንድንወጣ ውድድሮችን በገዛ ፈቃዳችን እንድንተው ለማድረግ የቻሉትን ሁሉ እያደረጉ ነው። ከዚያም ዞር ብለው፦ ‘አያችሁ? ዘዴው ሠርቷል’ ለማለት ነው” ብለዋል።

እንዲህ ዓይነቱ አካሄድ በገንዘብ መቀጣት ያለበት ሲሆን፤ ይህም ስልት ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል፤ ይህም ወደ 2 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ቅጣት ከተጣለበት በኋላ የሩሲያን ቡድን በድጋሚ እንዲሳተፍ ከፈቀደው የዊምብልደን ጉዳይ መረዳት ይቻላል ብለዋል።

የክሉዥ-ናፖካ ከተማ ከንቲባ ኤሚል ቦክ የሩሲያ ስፖርተኞች ብሔራዊ ምልክቶቻቸውን እንዳይይዙ ለማድረግ ማቀዳቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ፤ የሩሲያ የሪዝሚክ ጂምናስቲክ ቡድን በከተማዋ ከሚካሄደው የቻሌንጅ ካፕ ውድድር ራሱን ለማግለል ዐርብ ዕለት ወስኗል።

የቻሌንጅ ካፕ የመጨረሻው ምዕራፍ ውድድር ከሰኔ 19 እስከ 21 በሮማንያ ክሉዥ-ናፖካ ይካሄዳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0