በኬንያ የፋይናንስ ረቂቅ አዋጅ ተቃውሞ መታሰቢያ ሰልፍ ላይ ቢያንስ 355 ሰዎች ታሰሩ - የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር
19:05 25.06.2026 (የተሻሻለ: 19:14 25.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኬንያ የፋይናንስ ረቂቅ አዋጅ ተቃውሞ መታሰቢያ ሰልፍ ላይ ቢያንስ 355 ሰዎች ታሰሩ - የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር
▪ የአገር ውስጥ እና ብሔራዊ አስተዳደር ካቢኔ ጸሐፊ ኪፕቹምባ ሙርኮመን ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፤ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ ከ160 በላይ ተቃዋሚዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
▪ ፖሊስ በናይሮቢ የተሰበሰበውን ሕዝብ ለመበተን የአስለቃሽ ጭስ ጋዝ ጥቅም ላይ ማዋሉ ተዘግቧል።
▪ የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት በሀገሪቱ በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች በርካታ ታዋቂ አክቲቪስቶች እና ብሎገሮች ታስረዋል።
▪ እሥራቶች ቢኖሩም፤ ሙርኮመን ሰፊ የሆነ የዝርፊያ ወይም የንብረት ውድመት አለመኖሩን በማንሳት፣ ኬንያውያን ሰላምን በመጠበቃቸው አመስግነዋል።
▪ እንደ ባለሥልጣኑ ገለጻ፤ በሀገሪቱ በአጠቃላይ በአንጻራዊ ሁኔታ የተረጋጋ ሁኔታ የነበረ ቢሆንም፣ ጥቂት የወንጀል አካላት ግን ሰላማዊ ሰልፍን ሽፋን በማድረግ የተለያዩ ወንጀሎችን ለመፈጸም ሞክረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
© telegram sputnik_ethiopia