ቻይና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሚመራው የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ድል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች

ቻይና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሚመራው የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ድል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች
ቻይና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሚመራው የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ድል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 25.06.2026
ሰብስክራይብ
ቻይና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሚመራው የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ድል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጉዎ ጂያኩን ዛሬ ሐሙስ በሰጡት መግለጫ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ፓርቲያቸው 7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ በድጋሚ በማሸነፋቸው የእንኳን ደስ አላችሁ የአጋርነት መልዕክት አስተላልፈዋል።


ቻይና የኢትዮጵያ አስተማማኝ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን ጠቅሰው፤ ሀገሪቱ ከሁኔታዎቿ ጋር የሚስማማውን የልማት መስመር እንድትከተል እንደምትደግፍ ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።


አያይዘውም ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ላላት ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ዋጋ እንደምትሰጥና የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የደረሱባቸውን የጋራ ስምምነቶች እንዲሁም የቤጂንግ የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም ውሳኔዎችን ተግባራዊ ለማድረግ፣ ተግባራዊ ትብብርን ለማጠናከር እና ለደቡባዊው ዓለም አንድነት በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ ባደረገው አጠቃላይ የምርጫ ውጤት መሠረት፤ ገዥው የብልጽግና ፓርቲ 438 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበሮችን በከፍተኛ ድምፅ በማሸነፍ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይ ያለውን የበላይነት አስቀጥሏል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0