ቻይና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሚመራው የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ድል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች
17:55 25.06.2026 (የተሻሻለ: 18:14 25.06.2026)

ሰብስክራይብ
ቻይና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሚመራው የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ድል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጉዎ ጂያኩን ዛሬ ሐሙስ በሰጡት መግለጫ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ፓርቲያቸው 7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ በድጋሚ በማሸነፋቸው የእንኳን ደስ አላችሁ የአጋርነት መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቻይና የኢትዮጵያ አስተማማኝ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን ጠቅሰው፤ ሀገሪቱ ከሁኔታዎቿ ጋር የሚስማማውን የልማት መስመር እንድትከተል እንደምትደግፍ ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።
አያይዘውም ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ላላት ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ዋጋ እንደምትሰጥና የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የደረሱባቸውን የጋራ ስምምነቶች እንዲሁም የቤጂንግ የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም ውሳኔዎችን ተግባራዊ ለማድረግ፣ ተግባራዊ ትብብርን ለማጠናከር እና ለደቡባዊው ዓለም አንድነት በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ ባደረገው አጠቃላይ የምርጫ ውጤት መሠረት፤ ገዥው የብልጽግና ፓርቲ 438 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበሮችን በከፍተኛ ድምፅ በማሸነፍ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይ ያለውን የበላይነት አስቀጥሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጉዎ ጂያኩን ዛሬ ሐሙስ በሰጡት መግለጫ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ፓርቲያቸው 7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ በድጋሚ በማሸነፋቸው የእንኳን ደስ አላችሁ የአጋርነት መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቻይና የኢትዮጵያ አስተማማኝ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን ጠቅሰው፤ ሀገሪቱ ከሁኔታዎቿ ጋር የሚስማማውን የልማት መስመር እንድትከተል እንደምትደግፍ ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።
አያይዘውም ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ላላት ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ዋጋ እንደምትሰጥና የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የደረሱባቸውን የጋራ ስምምነቶች እንዲሁም የቤጂንግ የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም ውሳኔዎችን ተግባራዊ ለማድረግ፣ ተግባራዊ ትብብርን ለማጠናከር እና ለደቡባዊው ዓለም አንድነት በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ ባደረገው አጠቃላይ የምርጫ ውጤት መሠረት፤ ገዥው የብልጽግና ፓርቲ 438 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበሮችን በከፍተኛ ድምፅ በማሸነፍ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይ ያለውን የበላይነት አስቀጥሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X