ቡርኪና ፋሶ የአውሮፓ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ከአውሮፓ ሕብረት ልዩ መልዕክተኛ ጋር ሊደረግ የነበረን የውይይት ቀጠሮ ሰረዘች
17:27 25.06.2026 (የተሻሻለ: 17:34 25.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቡርኪና ፋሶ የአውሮፓ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ከአውሮፓ ሕብረት ልዩ መልዕክተኛ ጋር ሊደረግ የነበረን የውይይት ቀጠሮ ሰረዘች
ዦአው ክራቪንሆ ከበርካታ ከፍተኛ የቡርኪና ፋሶ ባለሥልጣናት ጋር ለመወያየት ወደ ኦጋዱጉ ባደረጉት ጉብኝት፤ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ሁሉንም የሥራ ቀጠሮዎቻቸውን እንደሰረዙባቸው የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ይህ ውሳኔ የተወሰደው፤ የአውሮፓ ፓርላማ ባለፈው ሰኔ 11 ቀን ቡርኪና ፋሶን በሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚከስ የውሳኔ ሐሳብ ማፅደቁን ተከትሎ እንደሆነ ተነግሯል።
የቡርኪና ፋሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በምላሹ የአውሮፓ ኅብረትን አምባሳደር ቢሯቸው በመጥራት የመንግሥታቸውን “ተቃውሞ፣ ቅሬታ እና ቅያሜ” ገልጸውላቸዋል።
ሆኖም እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ ከቡርኪና ፋሶ ባለሥልጣናት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።
ፎቶ፦ ዦአው ክራቪንሆ በየካቲት 2026 ኦጋዱጉን ሲጎበኙ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X