ሩሲያ ዓመቱን ሙሉ ለሚካሄድ የባሕር ላይ ትራንስፖርት የሚሆን የአርክቲክ ጋዝ ጫኝ መርከቦች እየገነባች ነው
13:05 25.06.2026 (የተሻሻለ: 13:14 25.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ ዓመቱን ሙሉ ለሚካሄድ የባሕር ላይ ትራንስፖርት የሚሆን የአርክቲክ ጋዝ ጫኝ መርከቦች እየገነባች ነው
ሁለተኛዋ በሩሲያ የተገነባችው የፈሳሽ ተፈጥሯዊ ጋዝ ጫኝ መርከብ ‘ኮንስታንቲን ፖስዬት’ በፕሪሞርስኪ ክራይ የስያሜ ሥነ-ሥርዓቷ ከተከናወነ በኋላ ሰኔ 11 ቀን አገልግሎት መስጠት ጀምራለች።
ይህች መርከብ እ.ኤ.አ. በታኅሣሥ 2025 ለአገልግሎት ከቀረበችው ‘አሌክሲ ኮሲጊን’ ከተባለችው የመጀመሪያዋ መርከብ ቀጥላ የተመረተች ናት።
በ‘አርክቲክ ኤልኤንጂ 2’ ፕሮጀክት አካልነት በዚቬዝዳ የመርከብ ማኑፋክቸሪንግ ጣቢያ ተጨማሪ መርከቦች በመገንባት ላይ ይገኛሉ።
ይህ የመርከብ ስብስብ የሩሲያን የአርክቲክ ሎጅስቲክስ ለማጠናከር የታለመ ሲሆን፤ አዲስ ትውልድ የበረዶ ደርማሽ የጭነት መርከቦችን በስፋት ወደ ማምረት የተደረገውን ሽግግር ያሳያል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X