ሁለት ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ቬንዙዌላን መቱ - የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ

ሰብስክራይብ

ሁለት ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ቬንዙዌላን መቱ - የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ

የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በሴኮንዶች ልዩነት ውስጥ ሁለት ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጦች በቬንዙዌላ የተከሰቱ ሲሆን፣ መጠናቸውም በሬክተር ስኬል 7.2 እና 7.5 ሆኖ ተመዝግቧል።

የስፑትኒክ ዘጋቢ እንደዘገበው፤ የመሬት መንቀጥቀጡ በካራካስ ከተማ በተለይም በቻካኦ ማዘጋጃ ቤት አልታሚራ አካባቢ በበርካታ ሕንጻዎች ላይ ከባድ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ አንዳንድ ሕንጻዎችም ፈርሰዋል።

ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በሲሞን ቦሊቫር ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ የደረሰውን ጉዳት እና ከርእደ-መሬቱ በኋላ ሰዎች በጎዳናዎች ላይ ተጠልለው እንደሚገኙ ያሳያሉ።

ባለሥልጣናት ነዋሪዎች በሕንጻዎች ውስጥ ወይም አስተማማኝ ባልሆኑ መዋቅሮች አቅራቢያ እንዳይቆዩ አሳስበዋል። እስካሁን ድረስ ስለደረሰው የጉዳት መጠን ይፋዊ መግለጫ አልተሰጠም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0