አፍሪካ ጥገኝነትን ሳይሆን በራስ መቆምን የሚያበረታቱ ሥርዓተ ትምህርቶች ያስፈልጓታል - ታንዛኒያዊ መምህር

ሰብስክራይብ

አፍሪካ ጥገኝነትን ሳይሆን በራስ መቆምን የሚያበረታቱ ሥርዓተ ትምህርቶች ያስፈልጓታል - ታንዛኒያዊ መምህር

​ አሁን ያሉ ሥርዓተ ትምህርቶች የጥገኝነት አስተሳሰብን የሚያሰርፁ በመሆናቸው፤ ራሳቸውን የሚችሉ ዜጎች ለማፍራት ማሻሻያ ማድረግ እንደሚገባ አቢሳይ ስቲቨን ንዛሊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

መምህሩ ያነሷቸው ዐቢይ ነጥቦች፦

​ ትምህርት፤ ተመራቂዎች ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ በቀጥታ በራሳቸው ሥራ እንዲሠማሩ የሚያስችላቸውን ተግባራዊ ክህሎት ከማስታጠቅ ይልቅ፤ በተግባር ያልተደገፈና ከመጠን በላይ ፅንሰ-ሀሳብ ላይ የተመሠረተ ሆኗል፣

​ ራሳቸውን የቻሉ ዜጎች የኢንዱስትሪ ዕድገትን ለማፋጠን፣ ለምርት ዕድገት እና ተጨማሪ መደበኛ ያልሆኑ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር የሚያስችሉ በመሆናቸው፤ የላቀ የኢኮኖሚ ነፃነት ይፈጥራሉ፣

​ በአፍሪካ ተጨባጭ እውነታዎች ላይ የተመሠረቱ ሥርዓተ ትምህርቶች፤ የቅጥር አስተሳሰብን በማስቀረት ተመራቂዎች አካባቢያዊ ችግሮችን የሚፈቱና ለማኅበረሰባቸው የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ የልማት ሞተሮች እንደሚያደርጋቸው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0