ጋናዊው ጠንቋይ እንግሊዝ ከጋና ጋር አቻ ለተለያየችበት የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ተጠያቂ ተደረገ

ሰብስክራይብ

ጋናዊው ጠንቋይ እንግሊዝ ከጋና ጋር አቻ ለተለያየችበት የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ተጠያቂ ተደረገ

 

​ናና ክዋኩ ቦንሳም ቀደም ብሎ የጋና ብሔራዊ ቡድን እንግሊዝን መቋቋም እንዲችል የእንግሊዝ ቡድን ኮከብ ሃሪ ኬን ላይ ድግምት አድርጌበታለሁ ማለቱን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

 

​“ሃሪ ኬን ላይ እየጠመጠምኩበት ነው። ምን ማድረግ እንደምችል ቀደም ሲል አሳይቻለሁ፤ ስለዚህ በሀገሬ ላይ ደምቆ እንዳይታይ ለመከላከል ምን ማድረግ እንዳለብኝ አውቃለሁ። ከባድ ጉዳት እንዲደርስበት አልፈልግም። በጨዋታው እሱን ማክሸፍ ብቻ በቂ ይሆናል። ጋናን ለመርዳት ሥራዬን እሠራለሁ" ሲል ቦንሳም ለአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ተናግሮ ነበር ተብሏል።

​ ጋና አቻ መውጣት በቻለችበት በዚህ ጨዋታ፤ ሃሪ ኬን ከጥቂት ርቀት የተገኘውን ግልጽ የግብ ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

​ እ.አ.አ በ2014 ቦንሳም የፖርቹጋሉ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ መጎዳት የእሱ ድግምት ውጤት መሆኑን ገልጾ የነበረ ቢሆንም፤ ተጫዋቹ በማገገሙ ምክንያት ድግምቱ "ሳይሠራ" መቅረቱን ሚዲያዎች አስታውሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0