የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ የአፍሪካ የወሳኝ ማዕድናት ብዝበዛ እንዲያበቃ ጥሪ አቀረቡ

ሰብስክራይብ

የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ የአፍሪካ የወሳኝ ማዕድናት ብዝበዛ እንዲያበቃ ጥሪ አቀረቡ

​ ፕሬዚዳንቱ ጥሪውን ያቀረቡት፤ የማዕድን ሚኒስትሮች ስብስብ የሆነውን የአፍሪካ ማዕድናት ስትራቴጂ ቡድን ልዑካን በቤተ-መንግሥታቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።

የቡድኑ የበላይ ጠባቂ ከሆኑት ፕሬዚዳንት ቲኑቡ ንግግር የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

​▪ "የቀረው ዓለም የእናንተ ሀገር የቆሻሻ ማጠራቀሚያ መሆኑ እንዲሁም ጥሬ ዕቃዎቻችሁን ያለክፍያ መመዝበሩ ግድ አይሰጠውም።"

​▪ ማዕድናት በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ምርምሮች፣ ልማቶችና ማጣራት አማካኝነት እሴት፣ ቴክኖሎጂ እና ብልጽግናን ማምጣት ይኖርባቸዋል።

​▪ ቲኑቡ በአኅጉሪቱ የሚደረጉ የማዕድን ልማት ውይይቶችን ማዕከላዊ ማድረግና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ መገንባት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

​በተጨማሪም፤ የቡድኑ አባላት በዓለም አቀፉ የማዕድን ገበያ ውስጥ የአፍሪካን የመደራደር አቅም እንዲያጠናክሩ አሳስበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0