የዩክሬን ጉዳይ አሁንም በፖለቲካዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ሊፈታ ይችላል - ላቭሮቭ
16:01 24.06.2026 (የተሻሻለ: 16:04 24.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዩክሬን ጉዳይ አሁንም በፖለቲካዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ሊፈታ ይችላል - ላቭሮቭ
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሞስኮ በተካሄደው "የፕሪማኮቭ ንባብ" መድረክ ላይ ያነሷቸው ሌሎች ነጥቦች፦
▪ ሩሲያ በማንኛውም ጊዜ በዩክሬን ጉዳይ ለመደራደር ዝግጁ ናት፤ ነገር ግን ጠረጴዛው ላይ የሚቀርበው ሐሳብ ከቁምነገር የሚገባ መሆን አለበት።
▪ ሩሲያ ለዩክሬን ቀውስ ጊዜያዊ መፍትሄዎችን አትቀበልም።
▪ የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አንቶኒዮ ኮስታ ተወካይ ከሞስኮ ተወካዮች ጋር ሁለት ጊዜ ግንኙነት አድርገዋል።
▪ ፓሪስ ለድርድር ተወካዮቿን ወደ ሞስኮ ልካለች፤ ከለንደን "ልዩ መልዕክተኞችም" ነበሩ።
▪ ሩሲያ ከዚህ በኋላ በዩክሬን ድርድር ዙሪያ የማንንም ቃል አታምንም።
▪ የፑቲንን ድጋፍ ያገኘው የአላስካ የአሜሪካ የሰላም ሐሳብ ላይ ሞስኮ እስካሁን ምንም ዓይነት ምላሽ አላገኘችም።
▪ ትራምፕ ዘለንስኪ በጥልቅ የሩሲያ ግዛቶች ጥቃት እንዲፈጽም ፈቅደዋል የሚሉ የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች፤ ምኞትን እንደ እውነታ አድርጎ ለማቅረብ የሚደረጉ ሙከራዎች ናቸው።
▪ የዊትኮፍ እና የኩሽነር የሞስኮ ጉብኝት በውይይት ላይ ነው፤ ሩሲያ ሐሳብቸውን ለመስማት ዝግጁ ናት።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X