ኬንያ የ1.2 ቢሊዮን ዶላር የናይሮቢ አውሮፕላን ማረፊያ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረመች
14:45 24.06.2026 (የተሻሻለ: 14:54 24.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኬንያ የ1.2 ቢሊዮን ዶላር የናይሮቢ አውሮፕላን ማረፊያ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረመች
የጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ለማዘመን ከቻይና ሮድ ኤንድ ብሪጅ ኮርፖሬሽን ጋር የተደረገው ስምምነት፤ “የኬንያን የምስራቅ አፍሪካ የኣቪዬሽን ማዕከልነት ደረጃ ለማጠናከር ያለመ” ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክት መሆኑን የሀገሪቱ የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴቪስ ቺርቺር በትናንትናው ዕለት ገልጸዋል።
የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ አድማስ፦
አዲስ የተርሚናል ሕንፃ እና ተያያዥ የድጋፍ መስጫ ተቋማትን መገንባት።
ነባር መሠረተ ልማቶችን ማዘመን እና ደረጃቸውን ማሻሻል፣
የአውሮፕላን ማረፊያውን የውስጥ እና የውጭ የአሠራር እንቅስቃሴዎችን ማሻሻል፣
አጠቃላይ የሥራ ቅልጥፍና እና የአገልግሎት አሰጣጥን ማሳደግ።
"የኬንያን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ተወዳዳሪነት ለማስቀጠል በግልጽነት፣ በተጠያቂነት እና ሁሉንም አስፈላጊ መስፈርቶች በጥብቅ በመከተል ረገድ ያለንን ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን" ሲሉም አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X