በሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ለወራት ቆማ የቆየችው የኢትዮጵያ መርከብ በሰላም ወደ ጂቡቲ ማቅናት እንደጀመረች ተገለጸ
14:30 24.06.2026 (የተሻሻለ: 14:34 24.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ለወራት ቆማ የቆየችው የኢትዮጵያ መርከብ በሰላም ወደ ጂቡቲ ማቅናት እንደጀመረች ተገለጸ
"ኤምቪ ጊቤ" የተሰኘችው መርከብ በእስራኤል እና ኢራን ግጭት ጉዞዋ ከተስተጓጎለ ወራት በኋላ በአሁኑ ወቅት በኦማን ባሕረ ሰላጤ አካባቢ እንደምትገኝ እና ወደ ጅቡቲ በመጓዝ ላይ መሆኗን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አስታውቋል።
መርከቧ እ.አ.አ ሰኔ 28 ከምሽቱ 2:00 አካባቢ ወደ መዳረሻዋ ጅቡቲ ወደብ ትደርሳለች ተብሎ እንደሚጠበቅም አገልግሎቱ ጨምሮ ገልጿል።
"ኤምቪ ጊቤ" በ347 ዓለም አቀፍ የወደብ መዳረሻዎች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከሚያውለበልቡ የኢትዮጵያ መርከቦች መካከል አንዷ ናት።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X