ኪም ጆንግ ኡን አዲስ ደምሳሽ የጦር መርከብ ወደ አገልግሎት አስገቡ

ሰብስክራይብ

ኪም ጆንግ ኡን አዲስ ደምሳሽ የጦር መርከብ ወደ አገልግሎት አስገቡ

​‘ቾይ ሂዮን’ የተሰኘው ባለ 5,000 ቶን ደምሳሽ የጦር መርከብ እያደገ የመጣውን የሀገሪቱን የባሕር ኃይል እና የኒውክሌር አቅም ማሳያ ነው ሲሉ ኪም ጆንግ ኡን ​በምዕራባዊቷ የወደብ ከተማ ናምፖ በተካሄደው የባሕር ኃይል ሥነ-ሥርዓት ላይ ተናግረዋል።

 

የመርከቡ ቁልፍ መገለጫዎች፦

​ የፀረ-አውሮፕላን እና የፀረ-መርከብ ጦር መሣሪያዎች ታጥቋል፣

​ ኒውክሌር መሸከም የሚችሉ ባሊስቲክ እና ክሩዝ ሚሳኤሎችን ታጥቋል፣

​ በቅርብ ወራት ውስጥ ከመርከቡ ላይ የተተኮሱ የክሩዝ ሚሳኤሎችን ጨምሮ በተሳካ ሁኔታ ሙከራ ተደርጎበታል።

ኪም በንግግራቸው፤ የሰሜን ኮሪያ የባሕር ኃይል አቅም ከእንግዲህ የባሕር ዳርቻዎቿን በመከላከል ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም ማለታቸውን ​የኮሪያ ማዕከላዊ የዜና ኤጀንሲ ዘግቧል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0