ምዕራባውያን ከአፍሪካ የላቀ ከፍተኛ የልማት ፈንድ ለዩክሬን መድበዋል - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

© telegram sputnik_ethiopiaምዕራባውያን ከአፍሪካ የላቀ ከፍተኛ የልማት ፈንድ ለዩክሬን መድበዋል - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ምዕራባውያን ከአፍሪካ የላቀ ከፍተኛ የልማት ፈንድ ለዩክሬን መድበዋል - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.06.2026
ሰብስክራይብ

ምዕራባውያን ከአፍሪካ የላቀ ከፍተኛ የልማት ፈንድ ለዩክሬን መድበዋል - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

​የኢኮኖሚ ትብብርና ልማት ድርጅት እና የአውሮፓ ኅብረት እ.ኤ.አ በ2025 ለዩክሬን የሰጡት "የልማት ድጋፍ" መጠን፤ ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ ሀገራት ከተመደበው እንደሚበልጥ የሩሲያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ግሩሽኮ ገልጸዋል።

​"በ2025 ለዩክሬን የተመደበው ይፋዊ የልማት ዕርዳታ 44.9 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን ይህም ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ ሀገራት ከተመደበው 29 ቢሊዮን ዶላር በእጅጉ የላቀ ነው" ብለዋል።

​ይህ የዕርዳታ አመዳደብ ሀብትን ወደ ግጭት የማዞር እንዲሁም ብቅ እያሉ ያሉ አዳዲስ የኃይል ማዕከላትን የማዳፈን አዝማሚያን የሚያሳይ ነው ሲሉ የሩሲያው ዲፕሎማት አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0