ምዕራባውያን ሀገራት ከሩሲያ ጋር ለሚደረግ ጦርነት በግልጽ እየተዘጋጁ ነው - ፑቲን
15:16 23.06.2026 (የተሻሻለ: 16:24 23.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ምዕራባውያን ሀገራት ከሩሲያ ጋር ለሚደረግ ጦርነት በግልጽ እየተዘጋጁ ነው - ፑቲን
ፕሬዝዳንቱ ከሩሲያ ከፍተኛ ወታደራዊ ትምህርት ቤት ተመራቂዎች ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይ ያነሷቸው ቁልፍ ነጥቦች፦
🟠 በተለያዩ አካባቢዎች የግጭት ተጋላጭነት እየጨመረ በመምጣቱ አሁን ያለው የዓለም ሁኔታ የተረጋጋ አይደለም፣
🟠 ምዕራባውያን ለጦረኝነታቸው ምክንያት ለማበጀት 'ሩሲያ ወታደራዊ ስጋት' ደቅናብናለች የሚሉ የሐሰት ክሶችን ይጠቀማሉ፣
🟠 ሩሲያ በባለብዙ ዋልታ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥርዓት ለሁሉም ወገን እኩልና የማይከፋፈል ደህንነት እንዲኖር ትሟገታለች፣
🟠 ሩሲያ ለውጫዊም ሆነ ውስጣዊ ስጋቶች ፈጣንና ተመጣጣኝ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ ናት፣
🟠 የሩሲያ ባለሦስት ክፍል የኒውክሌር ትጥቅ መዘመኑን ቀጥሏል።
🟠 ባለፈው ዓመት ከአንድ ሺህ በላይ የጦር መሣሪያዎችና የትጥቅ ዓይነቶች በጦርነት ሜዳ ላይ ተሞክረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X