ሩሲያ የአሜሪካ እና ኢራንን ስምምነት በማወደስ፤ በቀጣይ ውጤታማ ድርድር እንደምትጠብቅ ገለጸች

ሰብስክራይብ

ሩሲያ የአሜሪካ እና ኢራንን ስምምነት በማወደስ፤ በቀጣይ ውጤታማ ድርድር እንደምትጠብቅ ገለጸች

​"የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ አሁን ላይ ከየትኛውም ጉዳይ በላይ ሆኗል። ሩሲያ የተኩስ አቁሙን እና የአሜሪካ-ኢራን የመግባቢያ ሰነድ ፊርማን በደስታ ትቀበላለች። የተጀመሩት ድርድሮችም ውጤታማ እንደሚሆኑ ተስፋ እናደርጋለን" ሲሉ የክሬምሊን ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ተናግረዋል።

ረዳቱ ያነሷቸው ሌሎች ቁልፍ ነጥቦች፦

​ በኤቪያን በተካሄደው የቡድን ሰባት ጉባኤ ላይ የተሳተፉ የምዕራባውያን ሀገራት ጦርነቱን “እስከ መጨረሻው ዩክሬናዊ” ለመግፋት ሲሉ የ “አንኮሬጅ መንፈስን” ለማጥፋት የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል።

​ ጉባኤው በቀጠለው “የዩክሬን ድራማ” በምዕራባውያን ሀገራት መካከል ግልጽ የሚና መለዋወጥ የታየበት ነበር።

​ ሩሲያን ጨምሮ አብዛኛው የዓለም ክፍል በባለብዙ-ዋልታ ምኞቶች እና ምዕራባውያን በጫኑት “በሕግ ላይ የተመሠረተ ሥርዓት” መካከል የተከፋፈለውን ዓለም መቃኘቱን ይቀጥላል።

​ ክሬምሊን በኢራን ዙሪያ ያቀረበችው የኒውክሌር ጉዳይ ምክረ-ሐሳብ አሁንም እንዳለ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0