ናሚቢያ የስታርሊንክን የፈቃድ ጥያቄ በድጋሚ ውድቅ አደረገች

ሰብስክራይብ

ናሚቢያ የስታርሊንክን የፈቃድ ጥያቄ በድጋሚ ውድቅ አደረገች

ስታርሊንክ በናሚቢያ ውስጥ የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት ያቀረበውን የፈቃድ ማመልከቻ የሀገሪቱ የኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንዳደረገው የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

‍ ማመልከቻው ውድቅ የተደረገው ናሚቢያ ለዘርፉ ያወጣችውን ብሔራዊ የባለቤትነት መሥፈርት ባለማሟላቱ እንደሆነ ባለሥልጣኑ ገልጿል። በሀገሪቱ ሕግ መሠረት የትኛውም የቴሌኮም ኩባንያ ቢያንስ 51% ድርሻው በናሚቢያ ዜጎች ወይም በሀገር ውስጥ ኩባንያዎች መያዝ አለበት። የውጭ ሀገር ዜጎች በከፊልም ሆነ በሙሉ ባለቤት መሆን የሚችሉት በልዩ የመንግሥት ፈቃድ ብቻ ነው።

የናሚቢያ መንግሥት ይኸው የአሜሪካ ኩባንያ ወደ ሀገሪቱ የቴሌኮም ገበያ ለመግባት ያቀረበውን የመጀመሪያ ሙከራ ባለፈው መጋቢት ወር ውድቅ አድርጎት ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0