በፓኪስታን እና ኳታር አሸማጋይነት የተካሄደው የአሜሪካ-ኢራን ድርድር እንደተጠናቀቀ ቴህራን ገለጸች

© telegram sputnik_ethiopiaበፓኪስታን እና ኳታር አሸማጋይነት የተካሄደው የአሜሪካ-ኢራን ድርድር እንደተጠናቀቀ ቴህራን ገለጸች
በፓኪስታን እና ኳታር አሸማጋይነት የተካሄደው የአሜሪካ-ኢራን ድርድር እንደተጠናቀቀ ቴህራን ገለጸች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.06.2026
ሰብስክራይብ

በፓኪስታን እና ኳታር አሸማጋይነት የተካሄደው የአሜሪካ-ኢራን ድርድር እንደተጠናቀቀ ቴህራን ገለጸች

የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካዜም ጋሪባባዲ የ4ቱ ሀገራት የቴክኒክ ውይይት፤ ለቀጣዩ የከፍተኛ ደረጃ ድርድር ምዕራፍ መንገድ በመክፈት በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

የድርድሩ ዋና ዋና ውጤቶች፦

◼ ለኢራን የነዳጅ እና የፔትሮኬሚካል ምርቶች ሽያጭ አሜሪካ አጠቃላይ ፈቃድ ሰጥታለች (በውጭ ሀብቶች ቁጥጥር ጽ/ቤት ድረ-ገጽ ከወዲሁ ታትሟል)፣

◼ የታገዱ 12 ቢሊዮን ዶላር ሀብቶች እንዲለቀቁ የተወሰነው ውሳኔ (በሁለት ዙር ስድስት ስድስት ቢሊዮን ዶላር) አሁን ወደ ተግባራዊ ምዕራፍ ተሸጋግሯል፣

◼ በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ በኩል የሚጓዙ መርከቦች የደህንነት ጥበቃ ሥርዓት ጸድቋል፣

◼ በፓኪስታን እና ኳታር ተሳትፎ በሊባኖስ የግጭት መከላከያ ክፍል ተቋቁሟል፣

◼ ማዕቀብ ማንሳት፣ የኒውክሌር ጉዳዮች፣ መልሶ ግንባታና ኢኮኖሚያዊ ልማት እንዲሁም ክትትልና አፈጻጸምን የሚመለከቱ 4 የሥራ ቡድኖች ተዋቅረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0