በፓኪስታን እና ኳታር አሸማጋይነት የተካሄደው የአሜሪካ-ኢራን ድርድር እንደተጠናቀቀ ቴህራን ገለጸች
10:58 23.06.2026 (የተሻሻለ: 11:04 23.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በፓኪስታን እና ኳታር አሸማጋይነት የተካሄደው የአሜሪካ-ኢራን ድርድር እንደተጠናቀቀ ቴህራን ገለጸች
የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካዜም ጋሪባባዲ የ4ቱ ሀገራት የቴክኒክ ውይይት፤ ለቀጣዩ የከፍተኛ ደረጃ ድርድር ምዕራፍ መንገድ በመክፈት በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የድርድሩ ዋና ዋና ውጤቶች፦
◼ ለኢራን የነዳጅ እና የፔትሮኬሚካል ምርቶች ሽያጭ አሜሪካ አጠቃላይ ፈቃድ ሰጥታለች (በውጭ ሀብቶች ቁጥጥር ጽ/ቤት ድረ-ገጽ ከወዲሁ ታትሟል)፣
◼ የታገዱ 12 ቢሊዮን ዶላር ሀብቶች እንዲለቀቁ የተወሰነው ውሳኔ (በሁለት ዙር ስድስት ስድስት ቢሊዮን ዶላር) አሁን ወደ ተግባራዊ ምዕራፍ ተሸጋግሯል፣
◼ በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ በኩል የሚጓዙ መርከቦች የደህንነት ጥበቃ ሥርዓት ጸድቋል፣
◼ በፓኪስታን እና ኳታር ተሳትፎ በሊባኖስ የግጭት መከላከያ ክፍል ተቋቁሟል፣
◼ ማዕቀብ ማንሳት፣ የኒውክሌር ጉዳዮች፣ መልሶ ግንባታና ኢኮኖሚያዊ ልማት እንዲሁም ክትትልና አፈጻጸምን የሚመለከቱ 4 የሥራ ቡድኖች ተዋቅረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X