የአፍሪካ ቡድኖች በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ዓለምን እያስደመሙ ነው

© telegram sputnik_ethiopiaየአፍሪካ ቡድኖች በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ዓለምን እያስደመሙ ነው
የአፍሪካ ቡድኖች በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ዓለምን እያስደመሙ ነው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.06.2026
ሰብስክራይብ

የአፍሪካ ቡድኖች በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ዓለምን እያስደመሙ ነው

ካቦ ቨርዴ፦ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈችበት የዓለም ዋንጫ፤ የአውሮፓን ሻምፒዮኗን ስፔን 0ለ0 በሆነ አቻ ውጤት ማስቆም የቻለች ሲሆን በመቀጠል ከኡራጓይ ጋር 2 አቻ ተለያይታለች። ግብ ጠባቂያቸው ቮዚንሃ በዓለም መድረክ ላይ መነጋገሪያ መሆን ችሏል።

ሞሮኮ፦ ከኃያሏ ብራዚል ጋር 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ስትለያይ፤ ስኮትላንድን ደግሞ 1ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።

ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፦ ከ52 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫ የተመለሰችው ኮንጎ፤ በዮአን ዊሳ ታሪካዊ ግብ አማካኝነት ከፖርቹጋል ጋር 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይታለች።

ግብፅ፦ በዓለም እግር ኳስ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኙት ቡድኖች አንዷ የሆነችውን ቤልጂየምን 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ገታ፤ ኒውዚላንድን 3ለ1 ረትታለች።

ኮትዲቯር፦ አማድ ዲያሎ በ90ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት አስደናቂ የማሸነፊያ ግብ አማካኝነት ኢኳዶርን 1ለ0 በሆነ ጠባብ ውጤት አሸንፋለች።

ጋና፦ በ95ኛው ደቂቃ  ካሌብ ይሬንኪ ባስቆጠራት ወሳኝ ግብ ፓናማን 1ለ0 በማሸነፍ እጅግ አስፈላጊ ሦስት ነጥብ ማሳካት ችላለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0